image
image
image
image
image

በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ!" በሚል ርዕስ ለአባላት ሲሰጥ የነበረ ስልጠና ተጠናቀቀ።

ታህሳስ 1, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ለብልፅልግና ፓርቲ አባላት በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ!" በሚል ርዕስ ለአባላት ሲሰጥ የነበረ ስልጠና ተጠናቀቀ። የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስብሃት ስልጠናውን ሲያጠቃልሉ እንደገለፁት የማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ሀገርን ወደ ከፍታ የማሻገር ህልማችንን በጋራ በመሆን በመፍጠር ፣ በመፍጠን እና በመስፈንጠር የላቁ ድሎችን ማስመዝገብ የሚያስችሉ ፀጋዎች እና አቅሞች መኖራቸውን ገልፀው ከተሞች አዲስ አበባን ጨምሮ በፕላን ባለመመስረታቸው ተግዳሮቶች እንደነበሩ በተለይም የኮሪደር ልማት ከተሜነት ባህልን መገንባት የራሱን ገፅታ እንደፈጠረ ገልፀዋል። የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ብርሃኑ በበኩላቸው የገጠር ግብርና ትራንስፎርሜሽን ፣ የከተማ ልማት ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ዘርፎች ሀገራዊ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት እንዲሁም ለሌሎች ዘርፎች አስቻይ ሁኔታ በመፍጠር ለሀገረ መንግስት ግንባታ ትልቅ አቅም ስለሚፈጥሩ በስልጠናው ልዩ ትኩረት እንደተሰጣቸው ገልፀዋል። ውጥኖቻችንን ከግብ ለማድረስ የእያንዳንዳችን ድርሻ የላቀ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠናው ላይ ለተሳተፋ አባላት በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተግባቦት በመፍጠር ስልጠናው ተጠቃሏል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች